በቃልኪዳኑ መፈጸም ውስጥ የአርሱ ውለታ

የመፅሀፍ ቅዱስ መሰረት
"እግዚያብሔር ለአብርሀም ተገልጦ፣ ይህችን ምድር ለዘርህ እሰጣለሁ" አለው (ዘፍጥረት 12፣7፤15፣18-21)፡፡
"እግዚያብሔር ሙሴን እንዳዘዘው ለእስራኤል እንዲዋጉ ልባቸውን ያደነደነው ከእግዚያብሔር ዘንድ ነበር (እያሱ 11፣20)”፡፡
የእግዚያብሔር ቃልኪዳን እና የኔ ጉዞ
በእያሱ 11፤20 ያለውን ቃል ሳነበው፣ከእስራኤላውያን ተጋድሎ በላይ ነው የምረዳው፡፡የራሴ ህይወት የሚታየኝ፡፡ የእግዚያብሔር ቃልኪዳን እኔ ላሳካው ከምችለው በላይ ትልቅ ሆኖ ነው የሚታየኝ፡፡
ሁኔታዎቼን በማየት እንዲህ ያልኩባቸው ግዜያት ነበሩ "እግዚያብሔር በልቤ ያስቀመጠውን ለማድረግ በቂ ጉልበት ፣ልምድ እና ግብዓቶች የሉኝም"
ልክ እንደ እስራኤላዊያን ሁሉ፣ ከተጋፈጥኳቸው ግዙፋን ይልቅ ትንሽነት ተሰምቶኛል፤ከዋልታ ረገጥ የስሜት መለዋወጥ፣ የአዕምሮ ጭንቀት ትግል ጋር ይሁን ወይም ለመቋቋም ከሚከብድ እግዚአብሔርን የመጠበቅ ሁኔታ ውስጥ መሆን፡፡ እንደዛም ሆኖ እርሱ ለእስራኤላውያን እንደተዋጋው ሁሉ ለእኔም በዝምታ ሲዋጋልኝ አይቼዋለሁ፡፡ የቆምኩበት የከዳኘ በመሰለኝ ግዜ እንኳን፣ከመጋረጃው በስተጀርባ የድሌን መንገድ እያስተካከለልኝ ነበር፡፡
ሞገስ ስለእኔ ሳይሆን ስለእርሱ
እስራኤላውያን ከነዓንን የወረሱት ጠንካራ ጦር ስለነበራቸው ሳይሆን የእግዚያብሔር ቃልኪዳን ስለነበራቸው ነው፡፡ የኔም ታሪክ እንደዚሁ ነው፡፡
ያሉኝ ህልሞች፣የህይወት ጥሪ እና የተረዳኋቸው የውስጥ ፈውስ እንኳን ከእኔ ጥንካሬ የሆኑ አይደሉም፡፡እርዳታ ማለት የህይወቴ እውነታና ተግዳሮቶች በአንዴ ይጠፋሉ ማለት እንዳልሆነ መማር ነበረብኝ፡፡ይልቁንም የእግዚያብሔር ሀይል በህይወቴ መገለጥና የእርሱ ቃል ለውጤቱ ዋስትና መሆኑ ነው፡፡
በሆስፒታል ውስጥ እያነባሁ በምፀልይባቸው ግዚያት፣አእዕምሮዬ እረፍት የለሽ በሆነበት ግዜ እና ውስጤ ግልፅነት በፈለገባቸው ግዜያት የእርሱ እርዳታ ከእኔ ጋር ነበር፡፡ሁልግዜም የእርሱ ቃልኪዳን ከእኔ ህመም የበለጠ ነው፡፡
እርግጠኛ የሆንኩበት ውጤት
ወደኃላ ዞር ብዬ ሳየው፣መሰበር የነበረብኝ ቅፅበቶች ነበሩ ነገር ግን፣ የእግዚያብሔር አርዳታ አቁሞኛል፡፡ ጠላቶቼ ሊሰብሩኝ በሞከሩ ግዜ እርሱ ግን ድሌን እየፃፈልኝ ነበር፡፡ ታሪኬ ማብቃት በነበረበት ግዜ፣በቃልኪዳኑ አሳልፎኛል፡፡
በህይወቴ ላይ ያየሁት ውጤት የተረጋገጠ እንደነበረ አሁን ተገንዝቤያለሁ ፡፡እግዚያብሔር ቃል በገባልኝ ቅፅበት ለኔ የተረጋገጠ ነገር ነበር፡፡ እያነከስኩም ቢሆን እንኳን ወዳስቀመጠልኝ ስኬት ወደ ፊት መቀጠል ብቻ የነበረብኝ፡፡
የሙጥኝ ያልኩት ቃል
በመንገዴ ላይ ጌታ በጆሮዬ እንዲህ ሲል እሰማዋለሁ፡-


Comments